የምርምር ስነምግባር፣ የጥናታዊ ፅሁፎች ቅድመ ምርምር ግምገማና እዉቅና አሰጣጥ ቦርድ አሰራር

የምርምር ስነምግባር፣ የጥናታዊ ፅሁፎች ቅድመ ምርምር ግምገማና እዉቅና አሰጣጥ ቦርድ አሰራር እና የ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጥናታዊ ፅሁፎች መቀበያ ደህረ ገፅ ትዉዉቅና ስልጠና ተሰጠ፡፡

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት መከታተያ ጽ/ቤት ከግንቦት 20 አስከ 22/2018 ዓ.ም የምርምር ጽሁፍ ስነ ምግባርን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምርምር ጽሁፎች ጋር የተያያዙ የሥነ ምግባር ጉዳዮችን አንስቶ የተወያየ እንዲሁም አገልግሎቱን በማዘመንና ዲጂታላይዝ በማድረግ የግምገማ ሂደቱን የሚከወንበትን ድረ-ገጽንም አስተዋዉቋል።
የኢንስቲትዩቱ የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤት ዳይሬክተር ዶ/ር ማህደር ሚሊዮን በመድረኩ ላይጽ/ቤታቸው የተለያዩ የምርምር ጽሑፎች ከኢንስቲትዩቱም ሆነ ከሌሎች አጋር ተቋማት የሚመጡን የምርምር ስነምግባር ፋቃድ ጥያቄ በመገምገም ወደ ሥራ የሚያስገባ ጽ/ቤት መሆኑን ጠቅሰዉ በክልሎች ለሚገኙ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችና ጤና ቢሮዎች ለሚገኙ ባለሙያዎች የምርምር ጽሁፍን ሥነ-ምግባር አስመልክቶ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል:: የስልጠናው አላማም ከጽህፈት ቤታቸው ጋር በጋራ የሚሰራ ቦርድ (IRB) ፕሮፖዛሎችን የሚገመግምና አጽድቆ ምርምሮችን ወደ ሥራ እንዲገቡ የሚያደርግ ቦርድ ያላቸው ተቋማት ለሌሎች ልምድ የሚያካፍሉበት እና የሌላቸው ደግሞ የሚያቋቁሙበትን ሁኔታ መነሻ እውቀት እንዲቀስሙ ለማስቻል ሲሆን በመድረኩ ተቋማዊ የምርምር ጽሁፎች የግምገማ ቦርድ (Institutional Review Board) የሌላቸው የክልል የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የምርምር ስነምግባር መክታተያ ቦርዱ ማቋቋም የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይም ምክክር ተካሂዷል::
በምክክር መድረኩ አዳዲስ ከሥነ ምግባር የተያያዙ ጉዳዮችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የምርምር ፍቃድ ጽሑፎችንና ጥያቄ የሚላኩትም ድህረ ገፅ የሚተዋውቅበት መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በመስኩ በሙያ ልምዳቸው እና እውቀታቸው ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች የተሰጠ ሲሆን የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ተመራማሪ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታልየኢንስቲትዩቱ የምርምርሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤቱ ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ የምርምር ፁሑፎችን ገምግሞ ፍቃድ የሰጠና የአለም አቀፍ የምርምር ግምገማና ፍቃድ አሰጣጥ ስርዓትን በመከተል ከStratgic initiative for Developing Capacity in Ethical Review ( SIDCER) በ 2023 እ.ኢ.አ እዉቅና የተሰጠዉ ተቋም መሆኑ ይታወሳል::