ለላቦራቶሪ ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው

የኢንስቲትዩቱ የባክቴሪያል፣ፓራሳይቲክ እና እንሰሳት ነክ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት የወባና ትኩረት የሚሹ በሽታዎች ምርምር ቡደን በሃገር አቀፍ ደረጃ ፈጣን የወባ መመርመሪያ መሳሪያ የመመርመር ብቃትንና የባለሙያዎችን ክክሎትና ልምድ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ መረጃ ለሚሰበስቡ ከሁሉም ክልል ለተውጣጡ 38 የላቡራቶሪ ባለሙያዎች ከመጋቢት 3 እስከ 5/2012 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከል የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
የስልጠናው ዋና ዓላማ መረጃውን የሚሰበስቡ የላቡራቶሪ ባለሙያዎች ጥራቱን የጠበቀ መረጃ እንዲሰበስቡና መረጃ የሚሰበሰቡበትን የጤና ተቋም ባለሙያዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲሰጡ ለማድረግ ተገቢውን እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው ተፍልጎ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና ነው፡፡
በሀገር አቀፍ ደራጃ በተመረጡ ከ460 በላይ ከሚሆኑ የሄልዝ ፖስት መረጃው የሚሰበሰብ ሲሆን የወባ ፈጣን መመርመሪያ መሳሪያ የወባን በሽታ የመለየት እና የመስራት ብቃት እንዲሁም ባለሙያዎቹ በትክክል መሳሪያዎቹን ተጠቅመው በሽታውን እየለዩ ለመሆናቸው ስልጠናውን እየወሰዱ የሚገኙት የላቦራቶሪ ባለሙያዎች መረጃ እንደሚሰበስቡ ማወቅ ተችሏል፡፡
የተሰበሰበውም በረጃ ተተንተኖ የሚገኘውን ውጤት እና የሚታየውን ክፍተት መሰረት በማድረግ ኢንስቲትዩቱ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር አስፈላጊውን የቀጣይ ስራ ለመስራት ለውጣኔ ሃሳብ የሚቀርብ መሆኑን ስልጠናውን ከሚያስተባብሩት መረዳት ተችሏል፡፡