የወባ ፈጣን መመርመሪያ የማይለያቸው የተዋስያን ስርጭት በኢትዮጵያ ውስጥ ምን እንደሚመስል የምክክር መድረክ ተካሄደ

July 2, 2021
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የባክትሪያልፓራስቶሎጂ እና እንስሳት ነክ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት የወባ መመርመሪያ ተግዳሮቶችን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎች የማቅረብ የምክክር መድረክ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል፣ ከብሔራዊ ላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት፣ የምርምር ትግበራ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት እና የኢፒዲሞሎጂ የምርምር ቡድን በተገኙበት በአዳማ ከተማ ድሬ ሆቴል አካሄደ ።
መድረኩንም የኢንስትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አማካሪ ዶ/ር አሰፋ ደሬሳ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ በይፋ እስጀምረዋል።
የመድረኩ አላማም በወባ ምርመራ ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን መለየትና ለቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ ወባን ለማስወገድ እንዲጠቅሙ እና መሠረታዊ የሆነዉ የወባ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ማሻሻል፣ ብቁ ባለሙያዎችን መፍጠር እንዲሁም መሠረታዊ ልማቶችን ማብቃት መሆኑ ከመድረኩ ተገልፆ፤ የሚመለከታቸው አካላት ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።
የቀረቡ ጥናታዊ ፅሁፎችን መሰረት በማድረግ የተለያዩ አካላት ሀሳብ አስተያየቶችን አንስተው የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።